top of page

ርክክብ

 

ያኔ በዘመነ አዳም ሰዎች ያሹትን ሲበሉ፥
ምንም በማያውቀው ምስኪን በዲያብሎስ ያሳብባሉ።
ያኔ በዘመነ ቃየል ሰዎች ሰውን ሲቀሉ፥
በፈረደበት ሳጥናኤል በሰይጣን ያመሃኛሉ።

ዛሬ ደግሞ ሰው ሰልጥኖ፡
ሰው ሰይጥኖ፥
ከአጋሩ ከዲያብሎስ ስልጣን ግብሩን ተከፋፍሎ፥
ሃላፊነት መውሰድ ይዟል ጓዱን ገድሎ፥ 
ጓዱን ሰቅሎ።

የ ባህራን
ግንቦት 9 1999

bottom of page